1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የገንዘብ እርዳታ ለሰማዕታት ቤተሰቦች

ዓርብ፣ ሰኔ 26 2007

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቤተክህነት በተካሄደ ስነስርዓት ላይ እንደተገለፀው ስዊዝ ነዋሪ የሆኑት ኢትዮጵያውያን ሊቢያ ውስጥ በግፍ ለተገደሉት ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ሰማዕታት ቤተሰቦችና ወላጆች ከ400 ሺህ ብር በላይ ነው ያዋጡት።

https://p.dw.com/p/1FsII
Finanzielle Unterstützung für Familien in Ätiopien
ምስል DW/G. Tedla HG


በስዊዘርላንድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሁለት ወር በፊት ራሱን እስላማዊ መንግሥት ብሎ በሚጠራው ፅንፈኛ ቡድን ሊቢያ ውስጥ በአረመኔያዊ ግድያ ህይወታቸው ላለፈ ኢትዮጵያውያን ሰማዕታት ወላጆች እና ቤተሰቦች ያሰባሰቡትን ገንዘብ አበረከቱ። ትናንት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቤተክህነት በተካሄደ ስነስርዓት ላይ እንደተገለፀው ስዊዝ ነዋሪ የሆኑት ኢትዮጵያውያን ሊቢያ ውስጥ በግፍ ለተገደሉት ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ሰማዕታት ቤተሰቦችና ወላጆች ከ400 ሺህ ብር በላይ ነው ያዋጡት። በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኘው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ