የደቡብ ኢትዮጵያ ቀዉስ እና የኢሶዴፓ አቋም
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 24 2010ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ መስተዳድር በተለያዩ አካባቢዎች በተነሱ ግጭቶች ከቤት-ንብረቱ የተፈናቀለዉ ሕዝብ እስካሁን በቂ መጠለያ እና ድጋፍ አለማግኘቱን ተቃዋሚዉ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) አስታወቀ።የፓርቲዉ ምክትል ሊቀመንበር ጥላሁን እንደሻዉ እንደሚሉት ፓርቲያወቸዉ ለሕዝቡ እርዳታ ለማፈላለግም ሆነ በአካባቢዉ ለመንቀሳቀስ የወቅቱ ፖለቲካዊ ሁኔታ አልፈቀደለትም።ምክትል ፕሬዝደንቱ እንደሚሉት በደቡብ ኢትዮጵያ በሁለት ዞኖች በተቀሰቀሰዉ ግጭት እስከ መቶ ሺሕ የሚገመት ሕዝብ ተፈናቅሏል ተብሎ ይገመታል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ