ካሌ እና ስደተኞቿ
ሰኞ፣ ጥር 28 2010ማስታወቂያ
በፈረንሳይዋ የወደብ ከተማ ካሌ ባለፈው ሳምንት በስደተኞች መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት መብረዱ ተነገረ። ይሁን እና አሁንም በስፍራው ውጥረቱ ጋብ ያለ ቢመስልም በካሌ የስደተኞች ደህንነት አስጊ መሆኑን ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ስደተኞች ለዶቼቬለ ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንቱ ከአፍጋኒስታን ስደተኞች ጋር በተቀሰቀሰ ግጭት 5 ያህል የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው በጽኑ መቁሰላቸውን ከ20 በላይደግሞ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተዘግቧል። በስፍራው የነበሩ ስደተኞችን ያነጋገረችው የፓሪስዋ ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥሩነህ ተከታዩን ዘገባ ልካልናለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ኂሩት መለሰ