ማስታወቂያ
በቻይና የሚታገዘዉ የእስያ የመሠረተ ልማት መዋለ ንዋይ ባንክ «AIIB» ኢትዮጵያንና ካናዳን ጨምሮ 13 አዲስ አባል ሃገራትን ማካተቱ ተገለፀ።
ትናንት ከቀትር በኃላ ለንደን ከተማ በሚገኘዉ ፓርላማ አጠገብ የደረሰዉን ጥቃት ተከትሎ ራሱን እስላማዊ መንግሥት ብሎ የሚጠራዉ አሸባሪ ቡድን ኃላፊነትን ወሰደ። በቤልጂየም አንቬርፐን በተሰኘ ከተማ ሌላ የሽብርተና ጥቃት ከሸፈ።
የአዉሮጳ ኅብረት የዉጭ ጉዳይ ቢሮ የቱርኩን የአዉሮጳ ኅብረት ለማነጋገር ጠራ ። ኅብረቱ ከዲፕሎማቱ ጋር ዉይይት ያስፈለገዉ የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሪቺብ ታይብን ኤርዶዋን ከአንድ ቀን በፊት ያሰሙት የዛቻ ንግግርን ተከትሎ ነዉ።