Mantegaftot Sileshi Siyoumቅዳሜ፣ ሰኔ 18 2008የሶማሊያው ጽንፈኛ ታጣቂ ቡድን አል ሸባብ በመዲናይቱ ሞቃዲሾ የሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ የአጥፍቶ መጥፋት እና የተኩስ ጥቃት ዛሬ መፈጸሙን ተዘገበ። የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚዳንት ጄኮብ ዙማ በመቶዎች በሚቆጠሩ የሙስና ክሶች ዳግም ምርመራ እንዲደረግባቸው የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ያስተላለፈው ውሳኔ ላይ ያቀረቡት ይግባኝ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀረ። ብሪታንያ ከአውሮጳ ኅብረት ትውጣ ትቆይ በሚል ዳግም ሕዝበ-ውሳኔ እንዲደረግ የተጀመረው የፊርማ ማሰባሰብ ከ1,9 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገለጠ።