ማስታወቂያ
የምሽቱ አርስተ ዜና
በጋምቢያ የተቀሰቀሰዉ ፖለቲካዊ ቀዉስ እንደቀጠለ ነዉ። የሀገሪቱ ጦር ሠራዊት አዛዥ በዚህ የፖለቲካ ዉዝግብ ዉስጥ እሳቸዉም ሆነ ሠራዊታቸዉ እንደማይገባ አስታዉቀዋል።
በኢራን ዋና መዲና ቴህራን አንድ ፎቅ ቤት ላይ የተነሳን እሳት ለማጥፋት የተሰማሩ 30 የእሳት አደጋ ሠራተኞች በአደጋዉ ሞቱ።
ተሰናባቹ የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ትናንት ምሽት በሰጡት የመጨረሻ ጋዜጣዊ መግለጫ ነገ በይፋ ስልጣናቸዉን ለሚረከቡት ለተመራጩ የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ማሳሰብያ አስተላለፉ።