1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ለዉጥ

ማክሰኞ፣ ሰኔ 5 2010

በሥስት ቀናቱ ስብሰባ ከ120 ሐገራት እንደመጡ የሚገመቱ ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች ተካፍለዋል። በዘንድሮው መድረክ ላይ ከተካፈሉት ኢትዮጵያውያውያን መካከል የድረ ገጽ አምደኛው በፍቃዱ ኃይሉ እና የራድዮ ጋዜጠኛ ሲሳይ ውብሸት ወደ ስቱድዮአችን ብቅ ብለው ነበር።

https://p.dw.com/p/2zP5u
GMF Gäste aus Äthiopien
ምስል DW/T. Woldeyes

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ለውጥ እና መገናኛ ብዙሀን

ዶቼቬለ ያዘጋጀው  ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሀን መድረክ ዛሬም ለሁለተኛ ቀን እየተካሄደ ነው። የዘንድሮው ስብሰባ  መበላለጥ ወይም ልዩነቶች በሚታዩባት ዓለማችን የመገናኛ ብዙሀን አዘጋገብ እና ሚና ላይ ያተኮረ ነው። በሥስት ቀናቱ ስብሰባ  ከ120 ሐገራት እንደመጡ የሚገመቱ ከ2ሺህ በላይ ሰዎች ተካፍለዋል። በዘንድሮው መድረክ ላይ ከተካፈሉት ኢትዮጵያውያውያን መካከል ሁለቱ ዛሬ ወደ ስቱድዮአችን ብቅ ብለው ነበር።  እነርሱም የድረ ገጽ አምደኛው በፍቃዱ ኃይሉ እና የራድዮ ጋዜጠኛ ሲሳይ ውብሸት ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚደረገው ፈጣን ለውጥ እና ስለ መገናኛ ብዙሀን ይዞታ ኂሩት መለሰ አነጋግራቸዋለች። 

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ