የኢትዮጵያ የፖለቲካ ትኩሳት ከዬት ወዴት?
ማክሰኞ፣ የካቲት 13 2010ማስታወቂያ
ቀጣዩ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንሥትር ማን ሊኾን ይችላል? የበርካቶች መልስ ያልተገኘለት ጥያቄ ነው። ማን እንደሚኾን ከመገመት ባሻገር ግን በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም። በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ሀገሪቱ ጠቅላይ ሚንሥትሯ የሥልጣን መልቀቂያ ማስገባታቸው እና ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀባት መኾኗ ነው። የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች ቀጣዩን ጠቅላይ ሚንሥትር ለመምረጥ ንግግር እያደረጉ መኾናቸው ይነገራል። የትኛው ፓርቲ ከየትኛው ፓርቲ ጋር እየተነጋገረ ነው? የፖለቲካ ትኩሳቱስ አቅጣጫው ወደየት ነው የሚያመራው? ከፖለቲካ ተንታኙ ቻላቸው ታደሰ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገናል። ሙሉ ቃለ መጠይቁ ከታች የድምፅ ማጎeቀፉ ውስጥ ይገኛል።
ማንተጋፍቶት ስለሺ/ ቻላቸው ታደሰ
ኂሩት መለሰ