የኢትዮጵያ የዉጭ ጉዳይ እና የብሄራዊ ደህንነት ፖሊሲ
ረቡዕ፣ ኅዳር 13 2010ማስታወቂያ
The Indian Ocean news letter ለኢትዮጵያ መንግሥት ቅርበት ያላቸውን የመረጃ ምንጮች ጠቅሶ ኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ፖሊሲዋን ለማሻሻል ጥናት መጀመሯን ዘግቧል። በተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ ቋሚ ሚሲዮን ግን ሀገሪቱ ኤርትራን እና ደቡብ ሱዳንን በተመለከተ የፖሊሲ ጥናት ከመጀመሯ በስተቀር አሁን በተግባር ላይ የሚገኘውን የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ ሙሉ በሙሉ ሊቀይር የሚችል እቅድ በመንግስት በኩል እንደሌለ ገልጿል። የውጪ ጉዳይ ፖሊሲው ከወቅታዊው የአፍሪቃ ቀንድ ጂኦፖለቲካ አኳያ ያለበትን ተግዳሮት በተመለከተ ናትናኤል ወልዴ ከዋሽንግተን ዲሲ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ናትናኤል ወልዴ
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ