የሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ
ሰኞ፣ መስከረም 29 2010ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች እና የፌደሬሽን ምክር ቤቶች ዛሬ የሦስተኛ የሥራ ዘመን አንደኛ የጋራ ስብሰባቸውን ጀመሩ። የሁለቱ ምክር ቤቶች ስብሰባ የተጀመረው በኦሮምያ እና በሶማሌ ክልል ግጭት ህይወታቸውን ላጡ ሰዎች የህሊና ፀሎት በማድረግ ነበር። የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ያለፈውን ዓመት የመንግሥታቸው አፈጻጸም እና የወደፊቱን የትኩረት አቅጣጫዎች ጠቁመዋል። የሁለቱ ምክር ቤቶች ሥስተኛ የስራ ዘመን ከመጀመሩ ከአንድ ቀን አስቀድሞ ለ7 ዓመታት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሆነው ያገለገሉት አቶ አባዱላ ገመዳ የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባት ትኩረት ከሳቡት ጉዳዮች አንዱ ነበር። ስብሰባውን የተከታተተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን አጭር ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ