የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚያስገነባው ሆቴል
ረቡዕ፣ የካቲት 2 2008ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የራሱ የሆነ ባለ አራት ኮከብ ሆቴል እያስገነባ ነው። ይኽው በቻይና ኩባንያ በመሠራት ላይ የሚገኘዉ ሆቴል አየር መንገዱ፣ በኢትዮጵያ በኩል ወደ ሌሎች ሃገራት ለሚጓዙ መንገደኞች ማረፊያ የሚያወጣውን ወጪ እንደሚቀንስለትና ሥራውንም እንደሚያቀላጥፍ ተገልጿል። የአየር መንገዱ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ አየር መንገዱ የሆቴሉን አሰተዳድር ሆቴሎችን አወዳድሮ ለመስጠት ማቀዱን ተናግረዋል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ