1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ መንግሥት ርምጃና CPJ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 20 2008

በኮሚቴዉ መግለጫ መሠረት የኦሮሚያ ቴሌቪዥን ጣቢያ አዘጋጅ ፈቃዱ ሚርካና እና ነገረ-ኢትዮጵያ የተባለዉ ለተቃዋሚዉ ለሠማዊ ፓርቲ የወገነዉ አምደ መረብ ዋና አዘጋጅ ጌታቸዉ ሽፈራዉ የታሠሩበት ምክንያት ግልፅ አይደለም

https://p.dw.com/p/1HW6y

የኢትዮጵያ መንግሥት ጋዜጠኞችን ማሠሩን እና መረጃ የማግኘት መብትን መገደቡን እንዲያቆም ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ኮሚቴ አስታወቀ።በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ CPJ ተብሎ የሚጠራዉ ኮሚቴ እንዳስታወቀዉ የኢትዮጵያ መንግሥት ባንድ ሳምንት ዉስጥ ሁለት ጋዜጠኞችን አስሯል።በኮሚቴዉ መግለጫ መሠረት የኦሮሚያ ቴሌቪዥን ጣቢያ አዘጋጅ ፈቃዱ ሚርካና እና ነገረ-ኢትዮጵያ የተባለዉ ለተቃዋሚዉ ለሠማዊ ፓርቲ የወገነዉ አምደ መረብ ዋና አዘጋጅ ጌታቸዉ ሽፈራዉ የታሠሩበት ምክንያት ግልፅ አይደለም።የዋሽግተን ዲሲ ወኪላችን ናትናኤል ወልዴ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ናትናኤል ወልዴ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ