የአየር ንብረት ዉዝግብ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 6 2009ማስታወቂያ
ቦሎኛ-ኢጣሊያ የተደረገዉ የቡድን ሰባት አባል ሐገራት የተፈጥሮ ጥበቃ ሚኒስትሮች ስብሰባ እንደተፈራዉ በዉዝግብ ተጀምሮ በዉዝግብ ተጠናቅቋል።የስድስቱ ሐገራት ሚንስትሮች ከዚሕ ቀደም ፓሪስ ላይ የተፈረመዉን ዓለም አቀፍ ሥምምነት ገቢር ለማድረግ በድጋሚ ቃል ሲገቡ፤ የዩናይትድ ስቴትሱ መልዕክተኛ ግን ሥብሰባዉን አቋርጠዉ ወደ ሐገራቸዉ ተመልሰዋል።የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ሐገራቸዉ ከፓሪሱ ሥምምነት መወጣትዋን ካወጁ ወዲሕ ልዕለ ኃያሊቱ ሐገር ከነባር ተሻራኪና ተከታዮችዋ እየተነጠለች ነዉ።የሮሙ ወኪላችን ተክለ እግዚ ገብረየሱስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ተክለ እግዚ ገብረየሱስ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ