ኅብረቱ በኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንደሚያሳስበው ገልጿል
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 13 2010ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ኅብረት ከትላንት በስቲያ ባወጡት መግለጫ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እና በዩኒቨርስቲዎች እየታዩ ያሉት ሁከቶች እና ብሔር ተኮር ግጭቶች እንዳሳሰቡት ገልጿል፡፡ የክልልም ሆነ የፌዴራል የጸጥታ ኃይሎችም ከኃይል እርምጃ በመቆጠብ የዜጎቻቸውን ደህንነት እንዲጠብቁ ጠይቋል፡፡ የተፈጸሙትን ግድያዎች እና ወንጀሎች በገለልተኛ ወገን በማጣራት ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግም አሳስቧል፡፡ የብራስልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴ የላከውን ዝርዝር ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
ገበያው ንጉሴ
ሸዋዬ ለገሠ