1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኅዳር 29 ቀን 2009 ዓ,ም፤ የዓለም ዜና

ሐሙስ፣ ኅዳር 29 2009

https://p.dw.com/p/2Tysm

የዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት ከፍተኛ ባለስልጣናትና ከ 13 ሃገራት የተዉጣጡ አፍሪቃ ሃገራት መንግሥታት ባለስልጥናት አዲስ አበባ ላይ የሁለት ቀናት ዉይይት አካሄዱ። የፍርድ ቤቱ  አባላት አብዛኞቹ የአፍሪቃ ሃገራት መሆናቸዉ ይታወቃል።

 

የሰብዓዊ ጉዳዮች አያያዝ ላይ ለመምከር የጀርመንዋ መከላከያ ሚኒስቴር ኡርዙላ ፎን ደር ላይን በወግ አጥባቂ እስልምና መርህ የምትተዳደረዉን ስዑድ አረብያን ለመጀመርያ ጊዜ በመጎብኘት ላይ መሆናቸዉ ተገለጠ። በሃገሪቱ በያዝነዉ ዓመት ብቻ ከ 150 ሰዎች በላይ የግድያ ቅጣት ተፈጽሞባቸዋል።

 

በዓለማችን የሚገኙ ቀጭኔዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን በመቀነሱ የመጥፋት ስጋት እንደተጋረጠባቸዉ የዓለም የተፈጥሮ ጥበቃ ማኅበር ገለፀ። በመረጃዉ መሰረት በዓለም ዙርያ ያሉት ቀጭኔዎች ቁጥር 100 ሺህ አይበልጥም።