ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረዉ የራዕይ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ፤
ማክሰኞ፣ መስከረም 24 2009ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ራዕይ የተሰኘዉ የተቃዉሞ ፖለቲካ ፓርቲ በምህጻሩ ኢራፓ፤ በሀገሪቱ ስላለዉ ወቅታዊ ሁኔታ መግለጫ አሰራጨ። ኢራፓ ባሰራጨዉ አስር ገጽ በሚሆነዉ መግለጫዉ፤ ሀገሪቱ ዉስጥ የሚታየዉን ሕዝባዊ እንቅስቃሴና ተቃዉሞ ለማብረድ መንግሥት የሚሞክረዉ ጥገናዊ ለዉጥ እጅግም ዉጤት ሊያመጣ እንደማይችል፤ ይልቁንም በጠረጴዛ ዙሪያ ለሀገር በሚጠቅም ዉይይት ሌሎችም የሚሳተፉበት መንገድ ቢመቻች እንደሚበጅ ጠቁሟል። የፓርቲዉን ፕሬዝደንት ያነጋገረዉ ዘጋቢያችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ከአዲስ አበባ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ