1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ስምምነት

ዓርብ፣ የካቲት 30 2010

የሁለቱ ሐገራት ባለሥልጣናት በሌሎች ምጣኔ ሐብታዊ እና የንግድ ግንኙነቶች ላይም ተስማምተዋል።የሩሲያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካዉ አቻቸዉ የአዲስ አበባ ጉብኝታቸዉን እንዳጠናቀቁ ነዉ

https://p.dw.com/p/2u3cT
Äthiopien Besuch russischer Außenminister Sergei Lawrow mit Workneh Gebeyehu
ምስል Reuters/T. Negeri

(Beri.AA) Lavrove besuch in AA - MP3-Stereo

ሩሲያ ለኤሌክትሪክ ማመንጫ የሚረዳ የኑክሌር ጣቢያ ለኢትዮጵያ ለመገንባት ተስማማች።ዛሬ አዲስ አበባን የጎበኙት የሩሲያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ባደረጉት ዉይይት ከአዲስ አበባ በቀጥታ ወደ ሞስኮ የአዉሮፕላን በረራ እንዲደረግም ተስማምተዋል።የሁለቱ ሐገራት ባለሥልጣናት በሌሎች ምጣኔ ሐብታዊ እና የንግድ ግንኙነቶች ላይም ተስማምተዋል።የሩሲያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካዉ አቻቸዉ የአዲስ አበባ ጉብኝታቸዉን እንዳጠናቀቁ ነዉ።ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ነጋሽ መሐመድ