የነጋዴዎች አቤቱታ
ዓርብ፣ መስከረም 19 2010ማስታወቂያ
ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ቀፎዎች በኔትዎርኩ እንዲመዘገቡ ተግባራዊ ያደረገው አሠራር ከሥራ ውጭ አድርጎናል ሲሉ የሞባይል ቀፎ ነጋዴዎች አማረሩ። ነጋዴዎቹ በመደብሮቻቸው የሚገኙትን የሞባይል ቀፎች ሸጠው ሳይጨርሱ እንዲህ ዓይነት እርምጃ መውሰዱ ተገቢ አይደለም ሲሉ ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ በጉምሩክ በኩል ያላላፉ ቀፎዎች ከገበያ ውጭ መሆናቸው ግድ ነው ብሏል። ሁለቱንም ወገኖች ያነጋገረው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዘገባ አዘጋጅቷል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ