1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የምንያማር ቀውስ እና የኡንግ ሳን ሱ ኪ ምላሽ

ማክሰኞ፣ መስከረም 9 2010

የምናይማሯ መሪ ኡንግ ሳን ሱ ቺ በስተመጨረሻ በሮሒንጃያ ሙስሊሞች ላይ ሥለሚፈፀመዉ ግፍ  ዝምታቸውን ሰበሩ። የኖቤል ሽልማት ባለቤቷ ሱ ቺ የሐገራቸዉ ጦር የሚያደርሰዉን በደል እንዲያወግዙ የጠበቁ ግን አዝነውባቸዋል።

https://p.dw.com/p/2kJQ6
Myanmar Aung San Suu Kyi
ምስል Getty Images/AFP/Ye Aung Thu

የኡንግ ሳን ሱ ቺ ምላሽ

ሱ ቺ ዛሬ  ባደረጉት ንግግር የምያንያማርን ቀውስ ለማስወገድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያግዛቸው ይጠይቁ እናጂ የግድያ፤አስገድዶ መድፈር እና መንደር የማቃጠል ዘመቻ ያካሒዳል ተብሎ የሚወቀሰውን የአገራቸውን ጦር መተቸት አልሆነላቸውም። "ሁሉንም የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ኹከት እናወግዛለን" ያሉት ሱ ኪ በግጭቱ መከራ ለዘነበባቸው ሰዎች እናዝናለን ሲሉ አክለዋል። ሱ ቺ ዓለም በጉጉት የሚጠብቀውን ንግግር ሲያደርጉ ግን ከ400,000 በላይ የሮሒንጃያ የእስልምና እምነት ተከታዮች ከቀያቸው ተፈናቅለው ስደት ላይ ናቸው። የቡድሐ እምነት ተከታዮች የሚበዙበት የምንያማር መንግሥት በአናሳዎቹ የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ የሚፈፅመውን ተግባር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዘር ማጽዳት ሲል መኮነኑ አይዘነጋም። 

ገበያው ንጉሴ
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ