1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሙታን አያያዝ

ዓርብ፣ የካቲት 13 2007

በኢቦላ የተጠቁ ሰዎች ከሞቱ በኋላ የተሐዋሲው ዋነኛ አስተላላፊዎች በመሆናቸው አስክሬናቸው መነካት የለበትም። ሥርዓተ ቀብር መፈፀም ያለበት በሠለጠኑ ባለሙያዎች ነው።

https://p.dw.com/p/1Ef56
Sierra Leon Ebola Beerdigung Opfer 14.08.2014
ምስል AFP/Getty Images

ምዕራብ አፍሪቃ ውስጥ በባሕላዊ ሥርዓተ ቀብር ወቅት አስክሬኖችን በመሳም፣ በማጠብ አለያም በመንካት በርካታ ሰዎች በተሐዋሲው ሊጠቁ ችለዋል። በኢቦላ የተነሳ ከሞተ ሰው ቢያንስ አንድ ሜትር ያኽል መራቅ ያስፈልጋል።

በኢቦላ ታማሚ ጥቅም ላይ ውለው የነበሩ ፍራሾች፣ ልብሶች እና ሌሎች ቁሳቁሶች በአጠቃላይ የተሐዋሲውን ስርጭት ለመግታት ያስችል ዘንድ መቃጠል አለባቸው።

ሥርዓተ ቀብር መፈፀም ያለበት በሠለጠኑ ባለሙያዎች ነው። ጊኒ፣ ላይቤሪያ እና ሴራሊዮን ውስጥ በ24 ሠዓት የስልክ አገልግሎት ሊጠሩ የሚችሉ ባለሙያዎችን የቀይ መስቀል ድርጅት በልዩ ሁናቴ አሠልጥኗል። እነዚህ ባለሙያዎች ባህላዊ የእንጨት የሬሳ ሣጥኞችን የሚተኩ ማለትም አስክሬኖቹ ተጠቅልለው የሚቀበሩበት አለያም የሚቃጠሉበት ላስቲኮችን ያቀርባሉ። ምንም እንኳን ጥንቃቄ የተሞላበት አያያዝ ለሰዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆንም ሙታንም በክብር ሊስተናገዱ ይገባል። ያም በመሆኑ የጤና ባለሙያዎች ከክርስቲያን እና ከሙስሊም «የክብር ሥርዓተ ቀብር» ዓውድ አንፃርም መሰልጠን ይገባቸዋል።