1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የላይቤሪያ ፕሬዚደንት የኢትዮጵያ ጉብኝት

ማክሰኞ፣ የካቲት 21 2009

የላይቤሪያ ፕሬዚደንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ዛሬ በኢትዮጵያ የአራት ቀን ይፋ ጉብኝት ጀመሩ። ፕሬዚደንት ሰርሊፍ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ከፕሬዚደንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ እና ከጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በሀገሮቻቸው መካከል ስላለው ግንኙነት እና ስለአህጉራዊ ጉዳዮች ተወያይተዋል።

https://p.dw.com/p/2YOQh
Äthiopien Besuch Präsidentin Liberia Ellen Johnson Sirleaf
ምስል picture-alliance/abaca/M. W. Hailu

Ber. AA(Pr. Sirleaf Äthiopien Besuch) - MP3-Stereo

ከውይይቱ በኋላ ፕሬዚደንት ሰርሊፍ  ከጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በሰጡት በአፍሪቃው ያለውን የንግድ ልውውጥ ማሻሻል እንደሚያስፈልግ  ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያምም በተመድ የፀጥታው  ምክር ቤት ተለዋጭ አባልነ የሆነችው ኢትዮጵያ አፍሪቃን በሚመለከቱ፣ የአየር ንብረት ለውጥን በመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ የአህጉሩን የጋራ ድምጽ እንደምታሰማ እና ከላይቤሪያም ጋር በቅርብ እንደምትሰራ አስታውቀዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ

አዜብ ታደሰ