1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ2026 የዓለም ዋንጫ

ዓርብ፣ ሰኔ 8 2010

ትናንት ሞስኮ ላይ የተከፈተው 21ኛው የዓለም ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ዛሬም ቀጥሏል። ዛሬ የመጀመሪያ ጨዋታ ካደረጉት ዑራጓይ ግብፅን አንድ ለባዶ አሰናብቷል።

https://p.dw.com/p/2zdxS
FIFA-Kongress wählt Kanada, USA, Mexiko zu WM-Ausrichtern für 2026
ምስል Getty Images/AFP/K. Kudryavtsev

ካናዳ፣ አሜሪካ እና ሜክሲኮ ያስተናግዱታል

ኢራን እና ሞሮኮ  ደግሞ አንድ ለ ዜ  በሆነ ውጤት ጨዋታቸውን ቀጥለዋል። ቆየት ብሎ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ደግሞ ፓርቱጋል እና ስፔን ይጫወታሉ። ዘንድሮ ሩሲያ አስተናጋጅ ስትሆን ትናንት ሳዉዲን 5 ለባዶ ቀጥታለች። በነገራችን ላይ በቀጣይ ከስምንት ዓመት በኋላ የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅ ሞሮኮ ትሆናለች ተብሎ ሲጠበቅ፤ ሦስት ሃገራት በጋራ እንዲያዘጋጁ ተወስኗል። ዩናይትድ ስቴትስ ካናዳ እና ሜክሲኮ። ከዋሽንግተን መክብብ ሸዋ ኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ተጫዋጭ አሰልጣኞችን አስተያየት ያካተተ ዘገባ ይሎልናል።

መክብብ ሸዋ

ሸዋዬ ለገሠ