Tesfalem Waldyes Eragoማክሰኞ፣ ጥቅምት 28 2010የቀድሞው አንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት ወደ ሰማያዊ ፓርቲ መቀላቀላቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ በደርግ ጊዜ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሀገር በኃላፊነት ይሰሩ የነበሩ አቶ እሸቱ አለሙ የተባሉ ግለሰብ በኔዘርላንድስ ዘሄግ በሚገኝ ፍርድ ቤት ተከስሰው ጉዳያቸው በመታየት ላይ ይገኛል፡፡ የዛሬ የፍርድ ቤት ውሏቸውን አስመልክቶ ችሎቱን ከተከታተሉ ጋዜጠኛ ጋር ቃለ ምልልስ ይኖረናል፡፡ የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማንን የተመለከተ ዘገባም አለን፡፡ በጀርመን ቦን ከተማ ትላንት የተጀመረው እና ለቀጣዩቹ 10 ቀናት የሚቆየው የዓለም የከባቢ አየር ለውጥ ጉባኤንም እንዳስሳለን፡፡