ሐሙስ፣ ኅዳር 14 2010
በኢትዮጵያ የብቃት ምዘና ፈተና ወይም በተለምዶ COC ተብሎ የሚጠራዉን ስራ ላይ መዋል ከተጀመረ 10 ዓመት አስቆጥረዋል። በጤና፣ በሕግ እንዲሁም በቴክንክና ሙያ መስክ ያሉ ተማሪዎች አሁንም እየወሰዱ ይገኛሉ። ተማሪዎች ወደ ስራ ዓለም ከመግባታቸው በፊት በተማሩት የትምህርት መስክ የተማርዎቹን የaptitude/ስጦታ/፣ የክህሎትና የእዉቀት ደረጃ ለመመዘን ሲባል ፈተናዉ እንደሚሰጥ በትምህርት ሚንስቴር የፌዴራል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሙያ ደረጃና የብቃት ምዘና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ንግስት መላኩ ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል።
ፈተናዉን የሚፈተኑ ወይም የተፈተኑት ተማሪዎች ፈተናዉ ይዘት እነሱ ከተማሩት ጋር የተራራቀ እንደሆነ፣ ፈተናዉን ለመፈተን ወጭዉ ከአቅማቸዉ በላይ እንደሆነ እንድሁም ረጅም ጊዜ እንደምወስድ ቅሬታቸዉን ያሰማሉ።
ስማቸዉን ሳይጠቅሱ ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ከሆሳና ከተማ ለፈተናዉ የሚወጣዉን ወጭ በተመለከተ በዋትስኣፕ ላይ የድምጽ አስተያየታቸዉን ልኮውልናል።
ሌላ አሁን በሳዉድ አረቢያ የሚኖሩ አንድ ግለሰብ ለስደት ያበቃኝ COCን መዉደቀ ነዉ ይላሉ።
ምዘናዉ ረዥም ግዜ ይወስዳል መባሉን እንደማይቀበሉት ወ/ሮ ትግስት ይናገራሉ። በጀርመን አገር ምዘናዉ በዓመት ሁለቴ ብቻ እንደሚሰጥ የተናገሩት ወ/ሮ ትግስት ኤጀንስዉ ምዘና የሚያካሄደዉ በየሶስት ሳምንቱ ነዉ ይላሉ።
መርጋ ዮናስ
አርያም ተክሌ