ስነፍጥረት ሲመረመር
ረቡዕ፣ ሰኔ 3 2007ማስታወቂያ
Edwin Powell Hubble የተባለው አሜሪካዊ የሥነ ፈለክ ሊቅ እ ጎ አ በ 1929 ፣ ፍጥረተ ዓለም እየሠፋ ፤ እየተለጠጠ ፣ የሚሄድ መሆኑን በምርምር እንደደረሰበት አስገነዘበ። ቁስ አካል፤ ገዝፍ ያላቸው ነገሮች፤ ኅዋና ጊዜም ቢሆን ፣ ሁሉም መነሻ እንደነበራቸው አስረዳ። በኅዋ ፣ ከሜርኩሪ እስከ ኔፕቱን 8 ቱ ፕላኔቶች ፣ ከዋክብት ፤ በአጠቃላይ ፣ ፍኖተ ሃሊብ በተሰኘው ክፍል የሚገኙ ፀሐያዊ ጭፍሮች(ጋላክሲ) አንድ ብቻ ሳይሆን አያሌ ጋላክሲዎች መኖራቸውንም በተመራመረበት የሩቁን አጉልቶ በሚያሳይ ልዬ መነጽር (ቴሌስኮፕ) ረዳትነት አረጋገጠ። ኅዋ ፣ 13,7 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ዕድሜ አለው የተባለውም ከዚያ ምርምር ወዲህ ነው። በስማቸው የተጠራው ባለቴሌስኮፕ መንኮራኩር ፣ ወደኅዋ ዘልቆ በመግባት እስካሁን መረጃዎችን በማቅረብ ላይ ይገኛል። ዝርዝሩን ከድምጽ ዘገባዉ ያድምጡ
ተክሌ የኋላ
ነጋሽ መሐመድ