1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስርዓተ ፀሎት ለሚውኒክ የግድያ ሰለባዎች

ሰኞ፣ ሐምሌ 25 2008

የቀኝ ጽንፈኞችን አስተሳሰብ ያራምድ ነበር የተባለው የ18 ዓመቱ ኢራን ጀርመናዊ ወጣት ከአስር ቀን በፊት በጀርመን፣ የሚውኒክ ከተማ ለገደላቸው ዘጠኝ ሰለባዎች በትናንቱ ዕለት በከተማይቱ ስርዓት ፀሎት ተካሄደ። በዚሁ ስርዓተ ፀሎት ላይ ከሟች ቤተዘመዶች ጎን፣ የጀርመን ፕሬዚደንት ዮአኺም ጋውክ፣ መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል፣

https://p.dw.com/p/1JZoV
Deutschland Gottesdienst für die Opfer des Amoklaufs von München
ምስል picture-alliance/AP Photo/M. Schrader

[No title]

እንዲሁም፣ የከተማይቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና የሀይማኖት ተወካዮችም ተገኝተዋል። በስነ ስርዓቱ ንግግር ያሰሙትም ሁሉ፣ የዶይቸ ቬለ የንስ ቲውሮ እንደዘገበው፣ ጀርመን ለወንጀለኞች እና ለሽብር ፈጣሪዎች እንደማትንበረከክ በመግለጽ፣ እሴቶችዋን ጠብቃ እንደምትቆይ አስታውቀዋል።


የንስ ቲውሮ/ይልማ ኃይለ ሚካኤል
አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ