ሜርክል ዳግም በመራሒተ መንግሥትነት ተመረጡ
ረቡዕ፣ መጋቢት 5 2010ማስታወቂያ
ላለፉት 12 ዓመታት በመራሔ መንግሥትነት ያገለገሉት አንጌላ ሜርክል ለተጨማሪ አራት ዓመታት ዘመነ ሥልጣን ተመርጠዋል። መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል እንደተፈራዉ ሳይሆን በ 364 የምክር ቤት አባላት ድምፅ ነዉ የተመረጡት። አንዳንድ የሶሻል ዲሞክራት ፓርቲ አባሎች ድርጅታቸዉን ለማናደድ መራጮቻቸዉንም ለማስደሰት በዛሬዉ ምርጫ ድምፃቸዉን ይነፍጋሉ ተብሎ ተገምቶም ነበር። ሜርክል ከካቢኔ አባሎቻቸዉ ጋር ለሃገር ጥቅም፤ ህዝብ እና ለሃገሪቱ ደህንነት እስከ መጨረሻዉ ድረስ ለመስራት ቃለ ገብተዋል።አንጌላ ሜርክል ማን ናቸዉ ? ከምን ተነስተዉ እዚህ ቦታ የደረሱት? በመጭዉ አራት አመት የስልጣን ዘመናቸዉ ምን አዲስ የፖለቲካ ግብ ይኖራል ? የዶቼ ቬለዎቹ ይልማ ኃይለሚካኤልና ቢንያሚን ክኔት ዘገባ አዘጋጅተዋል ይልማ ያቀርበዋል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
አዜብ ታደሰ