3ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተከሳሾች እና ብይናቸው
ማክሰኞ፣ የካቲት 5 2005ማስታወቂያ
በዋሽንግተን በሚገኘው የአየር እና የኅዋ ቤተ መዝክር በሆነው በስሚዝሶንያን ሚውዝየም የአውቶሞቢል ማቆሚያ ሥፍራ ወይም ፓርኪንግ ሎት ይሰሩ የነበሩ ሦስት ትውልደ ኢትዮጵያውያን፡ ማለትም፡ ሁለት ሴቶች እና አንድ ወንድ፡ ከአንድ ነጥብ አምስት ሚልዮን ዶላር በላይ አጭበርብረዋል በሚል ተከሰው ጥፋተኛ መሆናቸው ተረጋግጦባቸዋል። ሁለቱ የእሥራት ቅጣት እና የወሰዱትን ገንዘብ እንዲከፍሉ ሲፈረድባቸው አንዷ ብይኑ ሳይሰጥ በፊት ሕይወቷን አጥፍታለች። እነዚህ ሦስት ግለሰቦች በስንት ዓመት ይህን ያህል ገንዘብ ከድርጅቱ ሊያጭበረብሩ ቻሉ? በምን ዓይነት ዘዴስ ተጠቀሙ?
አበበ ፈለቀ
አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ