1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

1434ኛ የኢድ አል አድሐ በዓል

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 5 2006

የ1434ኛ የኢድ አል አድሀ በዓል የስግደት ስነ ስርዓት ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲዮም ተከናወነ።

https://p.dw.com/p/19zrn
Eid Al Adha_Fest in Äthiopien, in Addis Abeba, Äthiopien, 15,10.2013 zugeliefert von: Ayram Abraha copyright: DW/Getachew Tedla
ምስል DW/G. Tedla

በበዓሉ አከባበር ወቅት እንደወትሮው በርካታ አማኞች በስፍራው አለመገኘታቸውን እና በቀዘቀዘ ሁኔታ መጠናቀቁንን ከዚያ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ የበዓሉን ስነ ስርዓቱን ተከታትሎ አጭር ዘገባ ልኮልናል።

እንዲሁ የአዲስ አበባ ወኪላችን ዮሀንስ ገብረ እግዚአብሔር ወደ መርካቶ አካባቢ ተዘዋውሮ አንድ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኝ ቤተሰብን ጎብኝቷል። በዓሉን እንዴት እንዳከበሩ ዘገባው ያስቃኘናል።

ሌላው ዘገባ ደግሞ የእስልምና እምነት ተከታዮች ቢችሉ በህይወት ዘመናቸው አንዴ የሚጓዙበት መካ ወደምትገኝበት ሳውዲ አረቢያ ይወስደናል። ዘንድሮም በሀጅ ፀሎት ላይ ለመሳተፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያን ወደ ሳውዲ አረቢያ ተጉዘዋል። በዓሉን እንዴት አከበሩት? ምንስ ገጠማቸው? የጅዳ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ተከታትሎታል።

እነዚህን ሶስት ዘገባዎች ማድመጥ ይችላሉ።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ዮሀንስ ገብረ እግዚአብሔር

ነብዩ ሲራክ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ