ለሳምንታት የዘለቀ ደም አፋሳሽ አመፅ መካከለኛው አፍሪቃ የምትገኘው ሀገር፤ ብሩንዲን አጨናንቋል።የሀገሪቱ ጦር ከአማፂያን ጋር እየተታኮሰ በርካታ ሰዎች መሞታቸውም ተረጋግጧል። ከዚህም በተጨማሪ ማንነታቸው ያልታወቁ እና የወታደር የደንብ ልብስ የለበሱ ሰዎች በርካታ የመንግሥት ፓርቲ አባሎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
አፄ ቴዎድሮስ ሃገሬ በጠላት እጅ አትወድቅም ብለዉ ራሳቸዉን ከሰዉ በኋላ በ1868 ዓ.ም ከመቅደላ አምባ የተዘረፉት ቅርሶች በተለይ ከ500 በላይ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶች ያሉባቸዉ የብራና ጽሑፎች፤ ፤ የንጉሣውያን የወርቅ ዘውዶችና ጌጣ ጌጦች፣ እንዲሁም ወደ አስር የሚሆን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ታቦታት በእንግሊዝ የተለያዩ ሙዚየሞች ይገኛሉ።