አስቀያሚው ቀን-በባሕር ዳር
ከስድስት ወራት በፊት ከባሕር ዳር ከተማ ዳርቻ በሚገኘው ድልድይ በርካቶች የሰላም ምልክት የሆነውን የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው መንግሥትን እየተቃወሙ ተሻግረዋል። ተቃውሞው ከድልድዩ ትንሽ ራቅ ብሎ በ52 የጦር መሳሪያ ባልያዙ ሰዎች ላይ የጸጥታ አስከባሪዎች በከፈቱት የተኩስ እሩምታ ተበተነ። «የጸጥታ አስከባሪዎች ድንገት ከድልድዩ ብቅ ብለው ያለ ምክንያት በተቃውሞ ሰልፉ ላይ ተኩስ ከፈቱ።» ሲሉ አንድ ቄስ ዕለቱን ያስታውሱታል። «ለመተኮስ ምክንያት እየፈለጉ ነበር።» በማለትም ቄሱ ያክላሉ።