የጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ የአስመር ጉብኝትና የሕዝብ አስተያየት
ሰኞ፣ ሐምሌ 2 2010ማስታወቂያ
በዚህ ስምምነት ኢትዮጵያና ኤርትራ የነበሩበት ጦርነትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማብቃቱን በይፋም አዉጀዋል፤ በፊርማቸዉም አፅድቀዋል። ጠ/ሚ ዐብይ የኤርትራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ገብተዋል። ዶቼቬለ ያነጋገርናቸዉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንደሚሉት ኤርትራዉያን እና ኢትዮጵያዉያን ወንድማማች ሕዝቦች መሆናቸዉን ኤርትራዉያን አስመስክረዋል። በአስመራ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የተደረገው አቀባበል የእዚህ አንዱ ማሳያ ነዉ ብለዋል።
ዩሐንስ ገ/እግዚአብሔር
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ