«የኢትዮጵያ መንግስት ቃል ገብቶልናል» አረጋዊ
ዓርብ፣ ሰኔ 22 2010ማስታወቂያ
በስደት የተመሰረተዉ የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገባ አስታወቀ።የፓርቲዉ ሊቀመንበር እና የቀድሞዉ የሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሓት) መሥራች ዶክተር አረጋዊ በርሔ እንዳሉት ፓርቲዉ ሐገር ቤት ለመግባት የወሰነዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ የተጀመረዉን ለዉጥ ለማገዝ ነዉ።ኢትዮጵያ መግሥት ዋስትና ማግኘታቸዉንም ዶክተር አረጋዊ አስታዉቀዋል።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ ዶክተር አረጋዊን በስልክ አነጋግሯቸዋል።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ