1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የስደተኞችን ፍሰት ለመግታት ያለመዉ ጉባኤ

ሐሙስ፣ ሰኔ 29 2009

 በዛሬዉ ዕለት በተለያዩ ሁለት የአዉሮጳ ከተሞች አዉሮጳን በተለይም የአዉሮጳ መዳረሻ ወደሆነችዉ ጣሊያን የሚጎርፈዉን የስደተኛ ብዛት መግታት በሚቻልበት መንገድ ላይ ለመምከር ስብሰባዎች እየተካሄዱ ነዉ።

https://p.dw.com/p/2g5an
Migranten in Italien
ምስል picture-alliance/dpa/C. Fusco

mmt Q&A EU plan to help Italy - MP3-Stereo

የአዉሮጳ ኅብረት ሃገራት የሀገር ዉስጥ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢስቶኒያ ዋና ከተማ ታሊን ተሰባስበዉ በስደተኞች ብዛት የተጨነቀችዉ ጣሊያንን መርዳት በሚችሉበት መንገድ ላይ መክረዋል። ሮም ላይ ደግሞ የአዉሮጳ ኅብረት እና የአፍሪቃ ዲፕሎማቶች የተመድ እና የዓለም የስደተኞች ድርጅት ባለስልጣናት በተገኙበት በሜዲትራኒያን ባህር ላይ የሚታየዉን ቀዉስ የተመለከተ ዉይይት እያካሄዱ ነዉ። የአዉሮጳ ኅብረት የስደተኞች መብዛት ያስጨነቃት ጣሊያንን ለመርዳት ያቀርባል የተባለዉ አዲስ እቅድ ምን ምን ያካትታል በሚል ወደ ብራስልስ ደዉዬ ዘጋቢያችን ገበያዉ ንጉሤን ጠይቄዉ ነበር።

Doku - Flucht übers Mittelmeer
ምስል AP Photo/E. Morenatti

በሌላ በኩል ካለፈዉ ጥር ወር ወዲህ ከ80 ሺህ በላይ ስደተኞች ወደ ግዛቱ እንደገቡ የተገለጸዉ ጣሊያን የአዉሮጳ ኅብረት አባል አጋሮቿ አንድ መፍትሄ እንዲፈልጉ ከሰሙን ጥሪ አቅርባለች። ጣሊያን ባቀረበችዉ ጥያቄ መሠረት የጣሊያን፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሳምንቱ መጀመሪያ አስቀድመዉ የሜዲትራኒያንን ባህር አቋርጠዉ ወደ አዉሮጳ የሚፈልሱ ሰዎችን በተመለከተ የተቀናጀ እና ተጨባጭ ምላሽ ለመስጠት መክረዋል። መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም መፍትሄ የሚሉትን ሃሳብ እያቀረቡ ነዉ።  የሮሙ ዘጋቢያችን  ተከታዩን ልኮልናል

ገበያዉ ንጉሤ/ተኽለእዝጊ ገብረ ኢየሱስ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ