1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሕግ አስከባሪ ተቋማት ለሕግ ተገዢ መሆን አለባቸዉ።

ዓርብ፣ ሰኔ 22 2010

የጉባኤዉ ባለሥልጣናት በሰጡት መገለጫ ሕግ አስከባሪ ተቋማት ለሕግ ተገዢ እና የዜጎችን መብት ጠባቂ ሆነዉ ሊደራጁ ይገባል።ጉባኤዉ የኢትዮጵያ መንግሥት የፀረ-ሽብር ሕግን፤ የበጎ አድራጎት እና የፕሬስ ሕጎችን  እንዲሽር ጠይቋል

https://p.dw.com/p/30ZEl
Äthiopische Menschenrechte Pressekonferenz Addis Abeba 2018
ምስል DW/Y. Egziabahre

(Beri.AA) Human Right council-Statment - MP3-Stereo

የኢትዮጵያ የሕግ አስከባሪ አካላት እና ተቋማት በአዲስ መልክ እንዲደራጁ የሰብአዊ መብት ጉባኤ ዛሬ ጠየቀ።የጉባኤዉ ባለሥልጣናት በሰጡት መገለጫ ሕግ አስከባሪ ተቋማት ለሕግ ተገዢ እና የዜጎችን መብት ጠባቂ ሆነዉ ሊደራጁ ይገባል።ጉባኤዉ እንደሚለዉ የኢትዮጵያ መንግሥት የፀረ-ሽብር ሕግን፤ የበጎ አድራጎት እና የፕሬስ ሕጎችን  መሻር ወይም ማሻሻል አለበት።እስካሁን ያልተፈቱ እስረኞች እንዲለቀቁ፤ የተለቀቁትም ወደ ቀድሞ ሥራቸዉ እና ኑሯቸዉ እንዲመለሱ መንግሥት እገዛ ያደርግላቸዉ ዘንድ የሠመጉ መሪዎች ጠይቀዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ