እስከ ዛሬ ማምሻ በይቅርታ የተፈታ የለም።
ዓርብ፣ የካቲት 2 2010ማስታወቂያ
በይቅርታ እንዲፈቱ ተወስኖላቸዋል ከተባሉት ታራሚ እና ተጠርጣሪዎች መካከል እስከ ዛሬ ማምሻ ድረስ የተፈታ አለመኖሩን ወደ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት የተጓዘው የአዲስ አበባው ወኪላችን ገልጾልናል። መንግሥት እስረኞች እንዲፈቱ ወስኗል ከተባለ በኋላ ከዛሬ ጠዋት አንስቶ በማህበራዊ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ነዉ። በተለይ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ አንዷለም አራጌ ዛሬ እንዲፈርሙ ተሰጣቸው የተባለ ፎርም ይዘት ውዝግብ አስነስቶ መግባባት ላይ አለመድረሳቸው በማህበራዊ መገናኛ ብዙሀን አስነብበዋል። አንዳንድ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችም እስረኞችን በመፍታት ሂደት ተነሱ በተባሉ ውዝግቦች ላይ አስተያየት እየሰጡ ነው። ይህን እና ከእስረኞች መለቀቅ ጋር የተያያዙ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ወደ ቅሊንጦ ሄዶ የነበረውን የአዲስ አበባውን ዘጋቢያችንን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔርን በስልክ አነጋግረነዋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
አዜብ ታደሰ