1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የብራስልስ የመጀመሪያው ጥቁር ከንቲባ

ዓርብ፣ ጥቅምት 9 2011

ቤልጅግ የመጀመሪያውን ጥቁር ከንቲባ ለደቡብ ምዕራብ ብራስልስ ጋንሾረን ማዘጋጃ ቤት መርጣለች። በጎርጎሮሳዊው 1975 ዓ.ም በስደት ወደ ቤልጅግ የመጡት ተመራጩ ከንቲባ ፒየር ኮንፓኒ ባለፈው እሁድ በተካሄደው ምርጫ ከአጠቃላይ ድምጽ 28 በመቶ አግኝተዋል።

https://p.dw.com/p/36qpJ
SYMBOLBILD Belgischer Wahlbezirk Brüssel-Halle-Vilvoorde BHV wird gespalten
ምስል picture alliance/KEYSTONE

የብራስልስ የመጀመሪያው ጥቁር ከንቲባ

ቤልጅግ የመጀመሪያውን ጥቁር ከንቲባ ለደቡብ ምዕራብ ብራስልስ ጋንሾረን ማዘጋጃ ቤት መርጣለች። በጎርጎሮሳዊው 1975 ዓ.ም በስደት ወደ ቤልጅግ የመጡት ተመራጩ ከንቲባ ፒየር ኮንፓኒ ባለፈው እሁድ በተካሄደው ምርጫ ከአጠቃላይ ድምጽ 28 በመቶ አግኝተዋል።

ቡካቩ በተሰኘ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከተማ የተወለዱት ፒየር የዝነኛው እግር ኳስ ተጫዋችና አምበል ቪንሰንት ኮንፓኒ አባት ናቸው። ልጃቸው ቪንሰንት ለማንችስተር ሲቲና ለቤልጂግ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን የሚሰለፍ ወሳኝ ተጨዋች ነው። የሰሞኑ መነጋገሪያ ስለነበረው ስለእኚህ ከንቲባ ምርጫ የብራስልሱ ዘጋቢያችን ዳግማዊ ሲሳይ ተድላ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ዳግማዊ ሲሳይ
ተስፋለም ወልደየስ 
ሸዋዬ ለገሠ