1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኦሮሚያ የተካሄደው የስራ ማቆም አድማ

እሑድ፣ ነሐሴ 28 2009

በኢትዮጵያ አስር ወራት ጸንቶ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ  ባለፈው ሀምሌ 28 ፣ 2009 ዓም  ከተነሳ ከጥቂት ቀናት በኋላ ጀምሮ በብዙ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል አካባቢዎች የስራ ማቆም አድማ እና አልፎ አልፎ ያለመረጋጋት ታይቷል። የመጀመሪያው የስራ ማቆም አድማ አዋጁ ከተነሳ ከሁለት ሳምንት በኋላ በባህር ዳር ከተማ ነበር የተካሄደው።

https://p.dw.com/p/2jES4
Äthiopien Jimma Geschlossene Geschäfte
ምስል DW User via Whatsapp

ባለፈው ሳምንትም ከ2007 ዓም ወዲህ ተቃውሞ ባስተናገደው የኦሮሚያ ክልል ውስጥ፣ በብዙ አካባቢዎች ከነሀሴ 17 እስከ 21፣ 2009 ዓም በክልሉ የስራ ማቆም አድማ ተጠርቶ ነበር። ማንነታቸው ይፋ ያልተደረገ ከሀገር ውጭ እና ቄሮ በሚል መጠሪያ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ኃይላት በማኅበራዊ ደረ ገጾች የጠሩት የዚሁ የስራ ማቆሙ አድማ አስተባባሪዎች እንዳሉት፣  ለአምስት ቀናት ተጠርቶ የነበረው ይኸው የስራ ማቆም አድማ ያስቀመጣቸውን ዓላማዎች በማሳካቱ በሶስተኛው ቀን ፣ ነሀሴ 19፣ 2009 ዓም ተቋርጧል። በአድማው ሰበብ በብዙ የክልሉ አካባቢዎች የንግዱ እና የመጓጓዣው አገልግሎት ተቋርጦ ነበር፣ መንገዶች ተዘግተው እና ስራ ማቆም ባልፈለጉ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች አሽከርካሪዎች ላይም ጥቃት መጣሉ ተሰምቷል። በጅማ በአንድ የገበያ ቦታ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በጣሉት የእጅ ቦምብ  ቢያንስ 13 ሰዎች ቆስለዋል።  የስራ ማቆሙ አድማ፣ ምክንያቱ  እና ዓላማው የዛሬው ውይይት ርዕስ ነው።  

አርያም ተክሌ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ