1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሐረር ነዋሪዎች በህገወጥ ድርጊቶች መበራከት ስጋት ገብቷቸዋል

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 30 2011

በሐረር ከተማ የቡድን ዝርፊያን ጨምሮ በየቀኑ የሚስተዋሉ ህገወጥ ድርጊቶች መበራከታቸው ህብረተሰቡን በስጋት እንዲኖር አድርጎታል ሲሉ የከተማይቱ ነዋሪዎች ለDW ተናገሩ። የከተማይቱን ጸጥታ የማስከበር ድክመት እንዳለ የሚቀበለው የሐረሪ ክልል የፍትህ ቢሮ በበኩሉ ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

https://p.dw.com/p/3BCt6
Stadtmauer von Harar Stadt im Südosten von Äthiopien
ምስል Azeb Tadesse Hahn

የሐረር ነዋሪዎች በህገወጥ ድርጊቶች መበራከት ስጋት ገብቷቸዋል

በሐረር ከተማ የቡድን ዝርፊያን ጨምሮ በየቀኑ የሚስተዋሉ ህግ እና ስርዓትን ያልተከተሉ ድርጊቶች መበራከታቸው ህብረተሰቡን በስጋት እንዲኖር አድርጎታል ሲሉ የከተማይቱ ነዋሪዎች ለDW ተናገሩ። ነዋሪዎቹ የኮንደሚንየም ቤታቸው በህገወጦች ተሰብሮ እንተወሰደባቸው እና ከሚኖሩበት ቤት የቀበሌ ቤት በግዴታ እንዲለቅቁ መደረጋቸውን ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ህግ እና ጸጥታን የማስከበር ኃላፊነት ያለባቸው አካላትም ስራቸውን በአግባቡ አለመስራታቸው ችግሩን አባብሶታል ብለዋል። ችግሩ እንዳለ የሚቀበለው የሐረሪ ክልል የፍትህ ቢሮ በበኩሉ ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው ሲል ምላሽ ሰጥቷል። የድሬዳዋው ዘጋቢያችን መሳይ ተክሉ ወደ ሐረር ተጉዞ ያጠናቀረውን ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።  

መሳይ ተክሉ

ተስፋለም ወልደየስ 

አርያም ተክሌ