1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ልዩ ቃለ ምልልስ ከዶር ነጋሶ ጊዳዳ ጋር 

ሰኞ፣ የካቲት 5 2010

ለስድስት አመታት ኢትዮጵያን በፕሬዝዳንትነት የመሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የቀድሞው ፓርቲያቸው የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ካሳለፈው ውሳኔ በኋላ መነጋገሪያ ሆነዋል። ኦሕዴድ ላለፉት 13 አመታት በፕሬዝዳንትነት ላገለገሉበት ይገባቸው የነበሩ ጥቅማጥቆሞች ላልተከበሩላቸው ዶ/ር ነጋሶ እገዛ ለማድረግ ወስኗል።

https://p.dw.com/p/2sYWJ
Äthiopien Negaso Gidada
ምስል DW/Y.G. Egziabhare

ልዩ ቃለ ምልልስ ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋር 

ዶ/ር ነጋሶ እንደሚናገሩት እስከ ባለፈው አመት የሚከፈላቸው የጡረታ ገንዘብ 1750 ብር ብቻ ነበር። የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት የመጓጓዣ መኪና እንደሚገዛላቸው፣ በኢትዮጵያም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጪ የሕክምና ወጪያቸውን እንደሚሸፍንላቸው ቃል ገብቷል። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የመኖሪያ ቤት ተገኝቶ አነጋግሯቸዋል። 

ሙሉ ቃለ ምልልሱን ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኑ 


ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሠ