1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፓሪስ፤ የሽብር ሰለባዎችን አሰበች

እሑድ፣ ጥር 1 2008

ፈረንሳይ በእስላማዊ ታጣቂዎች የተገደሉ የሽብር ሰለባዎችን በሕሊና ጸሎት ዛሬ አሰበች። የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦሎንድ ፤ የፓሪስ ከተማ ከንቲባ አኔ ሒዳልጎ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት በማዕከላዊ ፓሪስ በሚገኘው የደ ሪፐብሊክ አደባባይ በጎርጎሮሳዊው 2015 ዓ.ም. በሽብር ህይወታቸውን ላጡ 150 ሰዎች ቋሚ መታሰቢያ ቆሟል።

https://p.dw.com/p/1Hb1p
Paris Trauerfeier Jahresgedächtnis Terroranschläge Hollande
ምስል Getty Images/AFP/T. Samson

በፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦሎንድ እና የፓሪስ ከተማ ከንቲባ አኔ ሒዳልጎ ይፋ በተደረገው ቋሚ መታሰቢያ «በዚህ ቦታ የፈረንሳይ ዜጎች በጥር እና ኅዳር የሽብር ሰለባ ለሆኑት ያላቸውን ክብር ይገልጣሉ» የሚል ጽሁፍ ሰፍሯል። ፕሬዝዳንቱም ይሁኑ የፓሪስ ከተማ ከንቲባ ግን በስፍራዉ አንድም ቃል አልተናገሩም። ከመታሰቢያ ስነ-ስርዓቱ መጠናቀቅ በኋላ በቴሌቭዥን ንግግር ያደረጉት ከንቲባዋ ግን «ፓሪስ ፈርታለች። ይሁንና አሁንም በጽናት ቆመናል።» ሲሉ ባለፈው የጎርጎሪዮሳዊ አመት የተፈጸሙ የሽብር ጥቃቶች በከተማዋ ላይ ያሳደሩትን ጫና አስታውሰዋል።

እሸቴ በቀለ

ሸዋዬ ለገሠ