1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፈረንሣይ፥ በሶሪያ የአየር ድብደባ ጀመረች

እሑድ፣ መስከረም 16 2008

ፈረንሳይ ራሱን «እስላማዊ መንግሥት» እያለ የሚጠራው ቡድን ላይ የመጀመሪያውን የአየር ድብደባ ሶርያ ውስጥ እሁድ ማኪያሄዷን ገለፀች። ከፓሪስ እንደተገለፀው የአየር ድብደባው የተኪያሄደው በአካባቢው ከሚገኙ ተባባሪዎች ጋር በመቀናጀት ነው።

https://p.dw.com/p/1GeNC
Frankreich Kampfjet Kampfflugzeug Rafale
ምስል picture-alliance/AP Photo/Bob Edme

ፈረንሳይ ተባባሪ ብሪታንያ በነሐሴ ወር መጨረሻ ነበር ሶርያ ውስጥ በአማፂው ቡድን ላይ ጥቃት መሰንዘር የጀመረችው። ብሪታንያና ፈረንሣይ የአይ ኤስ ቡድንን ለመዋጋት ዩናይትድ ስቴትስ ኢራቅ ውስጥ በምታኪያሂደው ትግል ቢጣመሩም ሶርያ ውስጥ በሚኪያሄደው የእርስ በዕርስ ጦርነት ግን ጣልቃ መግባቱን ሸሽተው ቆይተው ነበር።

በሌላ በኩል ሩስያ፣ ሶርያ፣ ኢራቅና ኢራን አሸባሪው የአማፂ ቡድንን በጋር ለመውጋት ትብብር መጀመራቸውን ይፋ አደረጉ። የኢራቅ ጦር እንደገለፀው አራቱገራት መረጃ የሚለዋወጡበት አንድ የጋራ ማዕከል መስርተዋል። ይህ አዲስ የትብብርራ ሩስያ በአካባቢው ያላትን ሚና ከፍ ያደርገዋል ተብሎ ይታመናል። ምዕራባውያን በተደጋጋሚ ሩስያ የሶርያው መሪ የበሽር አል አሳድን ጦር ትደግፋለች በሚል ሲወቅሷት ሰንብተዋል።

ልደት አበበ

ማንተጋፍቶት ስለሺ