1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፀረ ዘመናዊ ባርነት ትግል

ሰኞ፣ ጥቅምት 11 2006

በዓለም ላይ ሰላሳ ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በዘመናዊ ባርነት እንደሚማቅቁ ባርነትን ለማጥፋት የሚታገል አንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ባለፈው ሳምንት አስታውቆል።

https://p.dw.com/p/1A3L3
Poipet (Kambodscha): Kinder mit schwerbeladenen Handwagen auf dem Weg zum Markt in Poipet in Kambodscha, aufgenommen am Montag (23.02.2004). Während einer mehrtägigen Asienreise besuchte die Gattin des deutschen Bundespräsidenten, Christina Rau, als UNICEF-Schirmherrin die Grenzstadt Poipet zwischen Kambodscha und Thailand. Dabei suchte sie persönlichen Kontakt zu Kindern in sozialen Einrichtungen von Unicef-Projekten. Poipet ist Umschlagplatz für den Menschenhandel: Jahr für Jahr werden Hunderte Jungen und Mädchen als Prostituierte, Arbeitskräfte oder Bettler nach Thailand verkauft. UNICEF hat ein Programm gestartet, um die Kinder zu betreuen und ihen ein neues Leben zu ermöglichen.
ምስል picture-alliance/ZB

« ዎክ ፍሪ ፋውንዴሽን» የተባለው ይኼው አዲስ ተቋም በርካታ መረጃዎችን አሰባስቧል። አላማው ዘመናዊውን ባርነት በተቻለ ፍጥነት ማስቀረት ነው።

ሊዊዘ የ 14 ዓመት ልጅ ነበረች ቀጣሪዋ የወሲብ ጥቃት ሲያሰርስባት እና ሲደበድባት። ይህም አልበቃ ብሎ አፍሪቃ የሚኖሩት ዘመዶቿ እንደተገደሉ ትሰማለች። ቀጣሪዋም ገዳዮቹን የላከው እሱ እንደሆነ ይነግራታል። ወጣቷ ከአንድ አመት በፊት ከምትኖርበት መንደር ወደ ጀርመን ስትመጣ ቀጣሪዋ ትምህርት ቤት እንደምትሄድ ነበር ቃል የገባላት፣እዚህ ስትመጣ ግን የጠበቃት ሌላ ነው። አማራጭ ያጣችው ወጣት ወደ ሴተኛ አዳሪነት ስራ ትገባለች።« ለሶስት አመት ያህል ደሙ አላቆመልኝም።»

ሊዊዘ በአሁኑ ሰዓት ደቡብ ጀርመን ውስጥ በሚገኝ ለተጎጂዎች በተዘጋጀ ማቆያ ትኖራለች። የበደል ጊዜው አልፎላታል። ይሁንና ሰላሳ ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በዓለም ላይ የዘመናዊ ባርነት ሰለባ እንደሆኑ ነው « ዎክ ፍሪ ፋውንዴሽን» የተሰኘዉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ድምዳሜ ላይ የደረሰው። በተለይ በአፍሪቃ እና በእስያ ለዘመናዊ ባርነት የሚዳረጉት ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ ነዉ። ሕንድ፥ ቻይና ፣ፓኪስታን እና ናይጄሪያ ቀዳሚውን ቦታ ይዘዋል። ሩስያም ከመጀመሪያዎቹ 10 ሀገሮች ተርታ ተሰልፋለች። ጥናቱ እንደሚያሳየው ከሆነም ማንኛውም አህጉር ይሁን ሀገር ከዘመናዊ ባርነት ነፃ አይደለም።

በሩሲያ የወሲብ ብዝበዛ ይደርሳል፣ በብራዚል በቤት ሰራተኞች ላይ ግፍ ይፈጸማል ። በቻይና የግዳጅ ስራ አለ፣ በህንድ እና ሄይቲም እንዲሁ ሰዎጥ ለባርነት ያዳረጋሉ ። የ« ዎክ ፍሪ ፋውንዴሽን» አጥኚ ኬቪን ባሌስ ለዶይቸ ቬለ በሰጡት መግለጫ፤

--- 2013_10_17_sklaverei.psd

የባርነት ዓይነቶችና እና መፍትሄዎቹ እንደ ሀገሩ ይለያያል ይላሉ ።«አንድ ወጥ መፍትሄ የሚሆን የለም። በየሀገሩ ያለውን ልዩ ሁኔታ መመልከት ያስፈልጋል። »

ስለ ዘመናዊ ባርነት ጥናት ያደረጉት ባገኙት ውጤት መሰረት ጀርመን ውስጥ 10,500 የሚሆኑ ሰዎች ከባርነት ጋር በሚስተካከል ሁኔታ ውስጥ ነው የሚኖሩት ። ኬቪን ባሌስ በእንዲሁ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ የሚገኙትን ሰዎች ትክክለኛ ቁጥሩ ማወቅ አስቸጋሪ ነው ይላሉ ። « የተሸፋፈነ የወንጀል ስራ ነው። ስለሆነም የወንጀሉን ብዛት ለማወቅ ከባድ ነው።»

መዘርዝር ሁሌም አሻሚ ነው። ተቋሙ ያገኛቸውን የተወሰኑ መረጃዎች ወስዶ በመላው ሀገር በዘመናዊ ባርነት ውስጥ የሚገኙት ቁጥር ይህን ያህል ነው ማለት ማነጋገሩ አልቀረም። ባሌስ ለዚህ መልስ አላቸው። « ባርነት እንደ ተላላፊ በሽታ ነው። አመቺው ወይንም ትክክለኛውን ቁጥር እስክናገኝ የምንጠብቅ ከሆነ በመካከል በርካቶች በባርነት ይሰቃዩና ይሞታሉ። ማንም ሊረዳቸው አይችልም።»

« ቴሬ ደ ሆም ዶችላንድ» የተባለው ህፃናትን የሚረዳው የጀርመን ድርጅት ለመላው ዓለም ያሰባሰቡት መረጃ ጥሩ መሆኑን የህፃናት መብት ጉዳዮች ተመራማሪዋ -ባርባራ ኩበርስ ከዶይቸ ቬለ ጋ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ገልጸዋል። እንደሳቸው ከሆነ የተቋሙ የባርነትን ትንታኔ የሚወደስ ነው።« አንድን ሰው ግዳጅ ውስጥ የሚጥልን ነገር ሁሉ እንደ ባርነት ነው የሚመለከቱት። ለምሳሌ ያለ እድሜ ጋብቻ። ይህን ደግሞ እኛ በመልካም እናየዋለን።»

የአንዳንድ ሀገሮች አሀዝ መስተካከል ያለበት ቢሆንም በአጠቃላይ ተቋሙ ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጣው ዘገባ ግልፅ ነው ይላሉ ኩበርስ ። ይህ መሆኑ አንዳንድ መንግስታት በጥናቱ ላይ ትክክለኛውን ቁጥር ፍለጋ እንዲያስቡበት ምክንያት ይሆናል ባይ ናቸው ኩበርስ።

« ዎክ ፍሪ ፋውንዴሽን» እንደ ቢል ጌትስ ባሉ በርካታ ፤ሀብታቸው በቢሊዮን የሚቆጠሩ ባለሀብቶች እንደሚደገፍ የተቋሙ ቃል አቀባይ ገልፀዋል። የድርጅቱ አጥኚ ኬቪን ባሌስ ዓለም አቀፉ የባርነት መዘርዝር አሁን ባለበት ሁኔታ በየአመቱ ተሻሽሎ መቅረብ አለበት ይላሉ። አላማውም 30 ሚሊዮን ግድም የሚሆን ሰው በዘመናዊ ባርነት እንዳይማቅቅ ለማድረግ ሲሆን ፤ ምባልባትም ቁጥሩን በሚመጡት 30 ዓመታት ወደ በጥቂት ሺዎች የሚቆጠሩ ተበዳዮች ዝቅ ማድረግ ያቻላል ብለው ያምናሉ።

ክላውስ ያንስ

ልደት አበበ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ