1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጥንቃቄ ለአይናችን

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 13 2005

በአዳጊ ሀገሮች በርካታ ህዝብ ሊድን ወይም በቀላሉ ሊከላከሉት በሚቻል የአይን ህመም የአይን ብርሃኑን እንደሚያጣ መረጃዎች ያመለክታሉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ 1,2 ሚሊየን የአይን ብርሃናቸዉን ያጡ እንዲሁም 5 ሚሊዮን ገደማ ደግሞ የማየት ችግር ያለባቸዉ ወገኖች አሉ።

https://p.dw.com/p/16VKC
ምስል AP

በሀገሪቱ የዓይን ማዝ በሁለተኛ ደረጃ የሰዎችን የአይን ብርሃን አሳጥቶ ለአይነስዉርነት የሚዳርግ መሆኑም ተደርሶበታል። ORBIS ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሚሰጠዉ የዓይን ጤና አገልግሎት 132 ሺህ አዋቂዎችና ህፃት ምርመራ እንደተደረገላቸዉ፤ 480 ሺህ ያህሉ ደግሞ ህክምና እንዳገኙ በድረገፁ ላይ ያሰፈረዉ መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ ዉስጥ ስራ ከጀመር ከአስር ዓመት በላይ የሆነዉ ኦርቢስ ኢንተርናሽናል፤ በዚህ ጊዜ ዉስጥ ታዲያ አሳሳቢዉን የአይነስዉርነት መንስኤ አይነማዝን፤ የአይን ሞራ እና ሌሎች ችግሮችን ኅብረተሰቡ ዉስጥ ገብቶ ከማከም በተጨማሪም ለአይን ሃኪሞች የሙያ ማበልፀጊያ ስልጠናዎችን እያስፋፋ እንደሚገኝ የድርጅቱ ዳይሬክተር ዶክተር አለማየሁ ሲሳይ ይናገራሉ።

Sonia Sarwari
ምስል DW/H. Sirat

ሰዎች ለግል ንፅህና ቅድሚያ በመስጠት እጅና ፊታቸዉን አዘዉትረዉ መታጠብን እንዳይዘነጉ፤ አካባቢያቸዉንም ማፅዳቱ የአይን ማዝ በሽታን ለምታስተላለፈዉ ዝንብ እድሉን እንደሚነሳት ነዉ ያመለከቱት። አይነማዝ እንዲሁም የአይን ሞራ በርካቶችን ለአይነስዉርነት ሲዳርጉ እነዚህ የዓይን ጤና ችግሮችን በቀላሉ ማከም እንደሚቻል፤ ማየት የተሳናቸዉ ወገኖችም ብርሃን ዳግም የሚያገኙበት ሁኔታ ኢትዮጵያም ዉስጥ ተመቻችቷል።

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋድ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ