1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጥሩ ህይወት ፍለጋ

ዓርብ፣ ኅዳር 7 2005

አቡ ዳቢ የሚታተመው « THE NATIONAL» የሚባለው ጋዜጣ ባለፈው ሰኞ ባወጣው ዘገባ አንዲት የሀገሪቱ የተባበሩት አረብ ኤምራቶች ዜጋና የቤት እመቤት ኢትዮጵያዊ ሰራተኛዋን ደብድባ በመግደሏ ፍርድ ቤት ቀርባለች።

https://p.dw.com/p/16jy0
16.11.2009 DW-TV Global 3000 Hausmädchen
ምስል DW-TV

ለፍርድ በቀረበችበትም ወቅት ሰራተኛዋን መደብደቧን አምና ግን ለመግደል ፈልጋ እንዳልነበር ገልፃለች። ሰራተኛዋ ከመሞቷ 10 ቀናት በፊት ሟቿን በኮረንቲ ገመድ ገርፋ እስራት ነበር። ይህም አልበቃ ብሎ የፈላ ውሀ ደፍታባት አይኗ ውስጥ ደግሞ ቁንዶ በርበሬ ጨምራለች። ይህ ሁሉ የሆነው እሷ እንደምትለው፤ ሰራተኛዋ «ሰነፍ»ስለሆነች ነው።

ይህንን ስቃይ ማየት ያልቻለው የቀጣሪ ልጅ ታድያ ፖሊስ ጠርቶ እናቱን በፖሊስ ቁጥጥር ስር አውሏል። ስቃዮን መቋቋም ያልቻለችው ኢትዮጵያዊት ወጣት ግን በድብደባው በመጎዳቷ ህይወቷን አጥታለች።

In this picture made available by Masdar and dated Aug. 30, 2010 shows the dome or the Library building of the Masdar Institute of Science and Technology in Abu Dhabi, United Arab Emirates. (ddp images/AP Photo/Masdar-HO)
አቡ ዳቢምስል AP

እንደ ሂውማን ራይትስ ዎች ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተደጋጋሚ ለአመታት ከውጭ ሀገር የሚመጡ የቤት ሰራተኞች ላይ ስለሚፈፀሙ ጥቃቶች ሲመዘግቡ ቆይተዋል። የድርጅቱ የመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪቃ ምክትል ኃላፊ ናዲም ሀውሪ ፤ «በብዛት የሚታዩት ጉዳቶች፤ ደሞዝ ያለመክፈል፣ በቀጣሪዎች የሚደረጉ የኃይል ርምጃዎች፣ ሰራተኞቹ በሳምንት አንዴ ወይንም ጭራሽ ቤቱን ለቀው እንዳይሄዱ የማድረጉ ሁኔታ ፣ አገር ቤት ካሉ ቤተሰቦቻቸው ጋ እንዲገናኙ ያለመፍቀድ፤ በተጨማሪ በቃል እና በድርጊት የሚደረጉ ጉዳቶች፣ ከዛም አልፎ እስከ ወሲብ ጥቃት ይደርሳሉ ።» ይላሉ ሀውሪ

ARCHIV - Ein ausländischer Arbeiter fegt die Straße vor der Scheich-Said-Moschee in Abu Dhabi (Archivfoto vom 28.06.2009). Mehr als zehn Millionen ausländische Arbeiter schuften derzeit in den arabischen Golfstaaten. Ohne diese mehr oder weniger rechtlosen Niedriglohnarbeiter aus Asien, die oft mehr als zwölf Stunden pro Tag arbeiten, wäre das Wirtschaftswachstum nicht denkbar. Foto: Anne Beatrice Clasmann dpa (zu dpa-Korr.: "Hitzige Debatte um moderne Sklaverei am Golf" vom 11.06.2009) +++(c) dpa - Report+++ Schlagworte Straßenszene, Palmen, kuppel, Kopfbedeckung, Straßenfeger, Gestik, halten, Turm, Kopftuch, sklavLÆ, Politik, Arbeit, Gebäude
ሴቶች ብቻ ሳይሆኑ ወንዶችም በሰራተኝነት ወደ አረብ አገር ይሄዳሉ።ምስል picture-alliance/dpa

በቀጣሪ እና በተቀጣሪ መካከል ችላ ሊባል የማይገባው እና እስከ ጥል ድረስ የሚያደርሰው ዋና ምክንያት የቋንቋ ችግር ነው። በርካታ ከኢትዮጵያ የገጠሩ ክፍል ወደ አረብ ሀገር የሚሄዱ ወጣቶች፤ የአረብኛም ይሁን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ችሎታ የላቸውም። ከዚህም ረገድ በኤጀንሲም ይሁን በግል ቅድመ ዝግጅት ሲደረግ አይታይም። ለብዙዎች ዘመናዊው ሀገር መደናገር ገና ከሀገር ሳይወጡ አዲስ አበባ ይጀምራል። ሆኖም በየቀኑ ወደ አረብ አገር የሚሄደው ሰው ቁጥር ብዙ ነው።

አራት ሚሊዮን ነዋሪ ያላት ሊባኖስ 200 000 የሚሆኑ የውጭ ሀገር ሰራተኞች ይኖሩባታል። ለሰራተኞች መብት የሚታገሉት ሀገራት ግን ጥቂት ናቸው።

« በአንዳንድ አገሮች አንዳንድ መሻሻል አለ።ለምሳሌ ዮርዳኖስ ለቤት ሰራተኞች አዲስ ህግ አውጥታለች። ሊባኖስ የቤት ሰራተኞች መብት የሚከበርበትን ውል አፅድቃለች። ነገር ግን እነዚህ ህጋዊ መሳሪያዎች በተግባር ላይ አልዋሉም። »

Zwei Frauen betrachten die Auslagen in einem der zahlreichen Geschäfte des Gold-Souks in Dubai (Foto vom 28.02.2007). Das Stadtgebiet am Dubai Creek gilt als das eigentliche alte Zentrum von Dubai. Hier gibt es neben modernen Hochhäusern auch die historischen Gold - und Gewürz-Souks mit ihren zahlreichen Läden. Foto: Wolfgang Thieme +++(c) dpa - Report+++
ከዘመናዊ ፎቆች ጎን ዱባይ በወርቅ ትታወቃለች።ምስል picture-alliance/ dpa

አንዳንድ ጥቃት የደረሰባቸው ወጣት ሴቶች እንደሚገልፁት ወደ ኢትዮጵያ ኤምባሲ ሄደው ምንም አይነት ድጋፍ እንዳላገኙ ነው። ለመሆኑ ማነው ለዚህ ሁሉ ኃላፊነት መውሰድ ያለበት? ሀውሪ፤

« እንደሚመስለኝ ቀዳሚው ኃላፊነት ያለው እንግዳ ተቀባይ ሀገራት ጋ ነው። አንድ ጥቃት ከደረሰ ይህ የእንግዳ ተቀባይዋ ሀገር የፍትህ ሚንስቴር እና ፖሊስ ስራ ነው ። በመቀጠል የሚልኩት ሀገራት ኃላፊነት አለባቸው በአንዳንድ ሀገራት ለምሳሌ ፊሊፒንስ ኤምባሲ፤ መንገዶችን ሲያመቻች ተስተውሏል። ሌሎች ሀገሮች ኢትዮጵያን ጨምሮ ደካማ አቅራቦት ነው ያላቸው። አዳዲስ ሰራተኞችን በመላክ ላይ የሚገኙ እንደ ኔፓል እና ማዳጋስካር ያሉ ሀገራት ደግሞ ጭራሽ ኤምባሲም የላቸውም። »

ሳውዲ አረቢያ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ የቤት ሰራተኞችን ጉዳይ አስመልክቶ ለመጠየቅ በስልክም ይሁን በፁሁፍ ያቀረብንላቸው ጥያቄ እስካሁን መልስ አጥቷል።

የሂውማን ራይትስ ዎች የመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪቃ ምክትል ኃላፊ ናዲም ሀውሪ እንደሚሉት ከግንዛቤ ማስጨበጥ ያለፈ ስኬት ብዙም አይታይም።

« እንደሚመስለኝ በአካባቢው ስላለው ችግር ግንዛቤ እንዲገኝ ሆኗል። በርካታ የአካባቢው እና ወጣት ሰራተኞች ስላለው ግንዛቤ እንዲገኝ መንገድ ፈጥረዋል። ይህ አንድ ምልዕክት ይመስለኛል። ይሁንና በሀገራት ደረጃ መሻሻል አልተመለከትንም። እንደሚመስለኝ ችግሩ እንደ ችግር አልተቆጠረም። ምንም አይነት መፍትሄ የሚሆኑ ርምጃዎችም አልተወሰዱም።» የዶይቸ ቬለ ዘጋቢ ነብዩ ሲራክ በሳውዲ አረቢያ ሲኖር በርካታ በቤት ሰራተኝነት ሊሰሩ የመጡ ሴት ኢትዮጵያንን አግኝቷል። በአጠቃላይ ያሉበትን ሁኔታ ነግሮናል።

ልደት አበበ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ