ጁባ የተራገፈዉ የጦር መሳሪያ፥ሱዳንና የኢትዮጵያ
ዓርብ፣ ጥቅምት 7 2001ማስታወቂያ
አንድ የኢትዮጵያ አዉሮፕላን የጫነዉ የነብስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ደቡባዊ ሱዳን ጁባ መራገፉ የሱዳንን ማዕከላዊ መንግሥትና የኢትጵያን መንግሥት ግንኙነት አጠያያቂ አድርጎታል።መሳሪያዉ መራገፉ እንደተሰማ የሱዳን ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባለልሥጣናት በካርቱም የኢትጵያ አምባሳደር አቶ ዓሊ አብዶን አስጠርተዉ ሥለ ጉዳዩ ማብራሪያ ጠይቀዋል።አምባሳደር ዓሊ መሳሪያዉ ለትርዒት የተላከ ነዉ ባይ ናቸዉ።ነጋሽ መሐመድ አምባሳደር ዓሊን አነጋግሮ የሚከተለዉን ዘገባ አጠናቅሯል።