ጀርመን የምትሰጠው የደም ካሳ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 29 2002ማስታወቂያ
በዚሁ መሰረትም መንግስት ከሰለባዎቹ ቤተሰቦች ጠበቃ ጋር መነጋገር እንደሚጀምር የጀርመን መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናግረዋል ። የጥቃቱ ሰለባዎች እና የቤተሰቦቻቸው ጠበቃ ካሪም ፖፓል ፣ ጀርመን ለሰባ ስምንት ቤተሰቦች የደም ካሳ እንድትከፍል ጠይቀዋል ። እንደ ጠበቃ ፓፓል የነሀሴው የቦምብ ድብደባ ሰለባዎች 179 ሰላማዊ ሰዎች ሲሆኑ ከመካከላቸው 137 ቱ ሲገደሉ 20 ቆስለዋል 22 ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም ። ። ይሁንና በአየር ድብደባው የሞቱትን ሰዎች ቁጥር እንደሚያጣራ የገለፀው የጀርመን መንግስት ለአደጋው ሰለባዎችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ሶሶት ሚሊዮን ዩሮ ካሳ ሊከፍል ነው መባሉንም ግምት ነው ሲል አስተባብሏል ። ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ይልማ ኃይለ ሚካኤል ፣ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ