ጀርመንና የስዑዲ አረቢያ ግንኙነት
ሐሙስ፣ ግንቦት 19 2002ማስታወቂያ
የጀርመንዋ መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል በመካከለኛዉ ምሥራቅ የሚያደርጉትን ጉብኝት ቀጥለዉ ዛሬ ዶሐ-ቀጠር ገብተዋል።ሜርክል ዛሬ ወደ ዶሐ ከመሔዳቸዉ በፊት ከትናንት በስቲያና ትናንት ጂዳ-ስዑዲ አረቢያን ገብኝተዉ ነበር።ሜርክል በጂዳ ቆይታቸዉ ከስዑዲ አረቢያዉ ንጉስ አብደላሕ ጋር በሁለቱ ሀገሮች ግንኙነቶችና በአለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።እዚያዉ ጂዳ ዉስጥ በተሰየመዉ የጀርመንና የሳዑዲ አረቢያ የጋራ የንግድ ምክር ቤት ጉባኤ ላይም ተገኝተዋል። የጂዳዉ ወኪላችን ነቢዩ ሲራክ ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።
Nebyu Sirak
Negash Mohammed
Aryam Abraha