ጀርመንና ዘረኝነት
ማክሰኞ፣ ሰኔ 15 2002ማስታወቂያ
ልዩ አጥኚው ጊቱ ምዊጋይ እ.ጎ.አ ከ ሰኔ 22 እስከ ሐምሌ 1 ,2009 ዓም ድረስ የፌደራል ክፍለ ሐገራትና የማዘጋጃ ቤቶች ባለስልጣናትን ህግ አውጭዎችን እና ህግ አስፈፃሚዎችን ሰፊ ጊዜ ወስደው አነጋግረዋል ። በጀርመን ዘረኝነትን እና የውጭ ዜጎች የሚደርስባቸውን ጥላቻ ለማስወገድ የሚታገሉ የሲቪል ማሕበራት ፣ የአናሳ ነዋሪዎች ፣ የሀይማኖት ቡድናት ተወካዮችን እንዲሁም ከዘረኝነት እና ከዘር አድልዎ እና ከውጭ ዜጎች ጥላቻና ተያያዥ ችግሮች ሰለባዎች ጋርም ሀሳብ ተለዋውጠዋል ። ልዩ አጥኚው ሳምንት ጄኔቭ ውስጥ ባቀረቡት ባለ ሀያ ሁለት ገፅ የጥናት ዘገባ ከዘረኝነት ጋር የተያያዘ አድልዎችን ለመከላከል ጀርመን በቂ ዕርምጃ አለመውሰዷን አስታውቀዋል ።
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ