1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዶክተሮቿን ያጣችዉ አፍሪቃ

ረቡዕ፣ መጋቢት 3 2000

የዓለም የጤና ድርጅት ወደአራት ሚሊዮን የሚደርሱ የጤና ባለሙያዎች የዓለም ህዝብ የጤና ይዞታ ለማስተካከል እንደሚያስፈልጉ ይገልፃል።

https://p.dw.com/p/E0mZ
የሃኪም ያለህ...... (በደቡብ አፍሪቃ)
የሃኪም ያለህ...... (በደቡብ አፍሪቃ)ምስል picture-alliance / dpa/dpaweb
ከደቡብ አፍሪቃ አገራት ብቻ 10ሺ ዶክተሮች አገሮቻቸዉን ትተዉ ወይ አሜሪካ ወይ አዉሮፓ አለበለዚያም ህንድ ወስጥ እየሰሩ ናቸዉ። ኢትዮጵያን ስንወስድ ደግሞ አገሪቱ ወስጥ ከሚገኙት የጤና ዶክተሮች ይልቅ በአሜሪካ በመስራት ላይ ያሉት በቁጥር እንደሚበልጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የብሪታኒያዉ የህክምና መፅሄት እንደሚለዉ በአሜሪካ ለ1,000 ሰዎች ከዘጠኝ በላይ የሚሆኑ ነርሶች ይደርሳሉ፤